image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ በአንድ ጀንበር ለ1500 ዜጎች የስራ ዕድል ትስስር ተፈጠረ።

ህዳር 4, 2018
በክ/ከተማው በአንድ ጀንበር ብቻ ለ1500 ዜጎች የስራ ዕድል ትስስር ተፈጥሯል። የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍታለው ከፍያለው እንደተናገሩት አስተዳደሩ የስራ ዕድል ፈጠራን የትኩረት ማዕከል አድርጎ በመስራት ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሯል ብለው በዛሬው ዕለት የተፈጠረው የስራ ዕድል ትስስር የዚሁ ማሳያ ነው ሲሉ ገልፀዋል። አቶ ፍታለው አክለውም የኢትዮጲያን የከፍታ ጉዞ ማረጋገጥ የሚቻለው ወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ሲቻል ነው ብለው ለዚህም አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል። የልደታ ክ/ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ድሪብሳ በፕሮግራሙ ባስተላለፍት መልዕክት እንደተናገሩት በአንድ ጀንበር የስራ ዕድል ትስስር የተፈጠረላቸው 1500 ዜጎች በስራ ፈላጊነት ተመዝግበው ስልጠና የወሰዱ መሆናቸውን ገልፀው በዛሬው ዕለትም ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር የቅጥር ውል እንዲፈራረሙ እና ወደ ስራ እንዲሰማሩ ተደርጓል ሲሉ ገልፀዋል። በ2018 በጀት ዓመት "በአዲስ ዕይታ የልደታንጰከፍታን ማረጋገጥ" የሚል መርህን ተላብሰን በሰራናቸው የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግባራት በርካታ የክ/ከተማችን ወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚ ሆነዋል ያሉት አቶ አራርሳ ለአብነትም የፈጠርናቸው የስራ ዕድሎች ማሳያ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል። አስተዳደሩ ለስራ ዕድል ፈጠራ ልዩ ትኩረት በመስጠት ባለፍት 4 ወራት ብቻ ለ10 ሺህ 265 ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ተገልጿል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች