በልደታ ክ/ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ዋና ዋና አገልግሎቶች

1. በአካባቢ ብክለት እና ተጽእኖ ግምገማ ቡድን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
  • ስለአካባቢ ብክለት፣ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት
  • ብክለት በሚያደርሱ ተቋማት ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ ፣
  • የብክለት መጠን በመለካት እርምጃ መውሰድ ፣
  • የፕሮጀክቶችን የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነዶችን በመገምገምና መቆጣጠር የማስተካከያ ሀሳብ መስጠት
  • የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ እና የአካባቢ ተፅእኖ ክዋኔ ሪፖርት መከታተል
2. በአየር ንብረት ለውጥ ቡድን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
  • ስለአየር ንብረት ለውጥ፣ ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት፣
  • ለአየር ንብረት ለውጥን በዘርፍ መ/ቤቶች በዕቅድ መካተቱን ማረጋገጥ ፣
  • ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ተጋላጭ የህበረተስብ ክፍሎች ድጋፍና ክትትል ፣
  • የኢነርጂ ቴክኖሎጂዎችን የዲዛይንና የፕሮሞሽን ስራ በመስራት ለተጠቃሚዎች ማስፋፋት፥
3. በስርዓተ ምህዳርና ብዝሃ ህይወት አጠቃቀም እና ቁጥጥር ቡድን ስር የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • በፕላን ለአረንጓዴነት የተመላከቱ ቦታዎች ከህገ ወጥ ወረራ ስለመጠበቃቸው እና ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውን የቁጥጥር ስራዎችን ይሰራል፤
  • የአንጓዴ ቦታዎች ከወራሪ አረሞች፣ ከእጽዋት በሽታዎች እና ተባዮች መጠበቃቸውን በዳሰሳ ጥናት በመለየት የቁጥጥርና የክትትል ስራችዎችን ይሰራል፤
  • በክፍለ ከተማችን በአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በየዓመቱ የሚተከሉ ችግኞችን የጽድቀት መጠን ዳሰሳ ጥናቶችን በመስራት ግኝቱንና ውጤቱን ለከተማ ውበት ጽ/ቤት እና ለአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ያሳውቃል፤ በግኝቱ መሰረት የማስተካከያ እርምጃዎች መወሰዳቸውንም ይከታተላል፤
  • በዘርፉ ለተመረቁ እና በአረንጓዴ ልማት ስራዎች ላይ የማማከር አገልግሎት መሰጠት ለሚፈልጉ ባለሙያዎች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ይሰጣል፤
  • በአፈር መሸርሸር እና መከላት ምክንያት የተጎዱ ቦታዎችን በመለየት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እንዲደረጉ ለሚመለከተው አካል በሪፖርት ያውቃል ተግባራዊነቱንም ይከታተላል፤
  • በግል፣ በመንግስት፣ በማህበራትና በተቋማት ይዞታዎች ላይ የተተከሉ ዛፎች ለምርት ሲደርሱ፣ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ሲያደርሱ፣ ከመብራት ጋር ንክኪ ሲፈጥሩ እና መሰረተ ልማት የሚያበላሹ መሆናቸው በባለሙያ ከተረጋገጠ የቆረጣ እና የምልመላ ፈቃድ ይሰጣል፤
  • ለዛፍ ቆረጣ ከሚሰጥ ፈቃድ ላይ የሮያሊቲ ክፍያ ብር ገቢ በማሰባሰብ የመንግስትን ገቢ በማሳደግ ረገድ እና ደኖች ያላቸውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በመጨመር ስራዎችን ይሰራል፡፡
  • ስለ አካባቢ ጉዳዮች የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ የተለያዩ የግንዛቤ ስራዎችን ይሰራል፤
  1. ገጽ-1
  2. ገጽ-2