image
image
image
image
image

ጽ/ቤቱ የወንዝ ዳርቻ ጥበቃና ክልከላ የደንብ ቁጥር 180/2017 የተመለከተ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

ሚያዚያ 2, 2018
የህግ ጉዳይችንና መመሪያዎች ለህብረተሰቡ በማስገንዘብ ዜጎችን ከአላስፈላጊ ቅጣቶችና ርምጃዎች ለመጠበቅ እየሰሩ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት ገለጸ። የልደታ ክፍለ ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጋሻዬነህ ታፈሰ እንደተናገሩት በአዲስ አበባ የከተማዋን ገጽታ የሚለውጡና የሚያሳምሩ እንዲሁም የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ የልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው የሚሰሩ የልማት ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ወንዞችን በንጽህና መያዝና የወንዝ ዳርቻውዎችን ከብክለት መከላከል ይገባል ብለዋል። አቶ ጋሻዬነህ አክለውም የህግ ጉዳዮችንና መመሪያዎችን ለህብረተሰቡ በማስገንዘብ ከአላስፈላጊ ቅጣትና እርምጃዎች ለመጠበቅ፣ህግ የሚተላለፉትን ደግሞ አስተማሪ ቅጣት እንደሚቀጣ ገልጸው የደንብ ቁጥር 180/2017 መሠረት በወንዝ ዳርቻዎች ላይ በሚሰሩ ስራዎችና በወንዞች ጉዳት የሚያደርሱ አካላትን ጥቆማ በመስጠት ተጠያቂነትን ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ልማቶች በተለይም በወንዝ ዳርቻወች የሚከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑና ለረጅም ዓመታት ህብረተሰቡን መጥቀም እንዲችሉ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች በህብረተሰቡ ሊጠብቁ እንደሚገባ የገለጹት አቶ ጋሻየነህ ከተለያዩ ተቋማት የሚወጡ በካይ ፍሳሽና ኬሚካሎች፣ያለፈቃድ የታከመ ፈሳሽን ወደ ወንዝ መልቀቅ፣በካይ ፍሳሽን ከጎርፍ መውረጃ ጋር ማገናኘት እንዲሁም ኬሚካል ነክ ፍሳሾችን የማከሚያ ዘዴን ሳይጠቀሙና ሳይረጋገጥ ወደ ወንዝ መልቀቅ በወንዝ ዳርቻ ጥበቃና ክልከላን የተመለከተውን የደንብ ቁጥር 180/2017 መሠረት የተከለከለ መሆኑን በመገንዘብ ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት የመመሪያውን ተግባራዊነት እንዲረጋገጥ በመተባበር መስራትይገባል ብለዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች